1 |
ሳይከካ ተቦካ |
2 |
ቀና ሲታጣ ይመለመላል ጎባጣ |
3 |
አላዋቂ ሳሚ ንፍጥ ይለቀልቃል |
4 |
አባይ ማደሪያ የለው ግንድ ይዞ ይዞራል |
5 |
ያለ አንድ የላት ጥርስ በዘነዘና ትነቀስ |
6 |
የምታቦካው የላት የምትጋግረው አማራት |
7 |
የጅብ ፍቅር እስኪቸግር |
8 |
አላርፍ ያለች ጣት ስትጠነቁል ትያዛለች |
9 |
በሬ ከአራጁ ይውላል |
10 |
በቅሎ ግዙ ግዙ አንድ አሞሌ ጨው ላያግዙ |
11 |
ዘመድ ከዘመዱ አህያ ከአመዱ |
12 |
ሲሮጡ የታጠቁት ሲሮጡ ይፈታል |
13 |
አይጥ ሞቷን ስትሻ ሄዳ ታሸታለች የድመት አፍንጫ |
14 |
ከድጡ ወደ ማጡ |
15 |
የጅብ ችኩል ቀንድ ይነክሳል |
16 |
የነ ቶሎ ቶሎ ቤት ግድግዳው ሰንበሌጥ |
17 |
አፍንጫ ሲመታ አይን ያለቅሳል |
18 |
በሰው ቁስል እንጨት ስደድበት |
19 |
አልሸሹም ዞር አሉ |
20 |
ታጥቦ ጭቃ |
21 |
የቆጡን አወርዳለሁ ብላ የብብቷን ጣለች |
22 |
ለሰው ብሎ ሲያማ ለኔ ብለህ ስማ |
23 |
ወደሽ ከተደፋሽ ቢረግጡሽ አይከፋሽ |
24 |
ባጎረስኩት እጄ ምነው መነከሴ |
25 |
እጸድቅ ብዬ ባዝላት ተንጠልጥላ ቀረች |
26 |
ጅራፍ ራሱ ገርፎ ራሱ ይጮሀል |
27 |
ሳል ይዞ ስርቆት ቂም ይዞ ፀሎት |
28 |
ያዳቆነ ሰይጣን ሳያቀስ አይለቅም |
29 |
የማያጠግብ እንጀራ ከምጣዱ ያስታውቃል |
30 |
አያዘልቅ ፀሎት ለቅስፈት |
31 |
ከኑግ የተገኘህ ሰሊጥ አብረህ ተወቀጥ |
32 |
ሰርገኛ መጣ በርበሬ ቀንጥሱ |
33 |
ያልጠረጠረ ተመነጠረ |
34 |
አዛኝ ቅቤ አንጓች |
35 |
ላም ባልዋለበት ኩበት ለቀማ |
36 |
ላም አለኝ በሰማይ ወተቷንም አላይ |
37 |
ጊዜ የሰጠው ቅል ድንጋይ ይሰብራል |
38 |
አህያውን ፈርቶ ዳውላውን |
39 |
ሴት የላከው ሞት አይፈራም |
40 |
ሌባ ላመሉ ዳቦ ይልሳል |
41 |
ስራ ለሰሪው እሾህ ለአጣሪው |
42 |
አባቱ ዳኛ ልጁ ቀማኛ |
43 |
ተልባ ቢንጫጫ በአንድ ሙቀጫ |
44 |
አመድ በዱቄት ይስቃል |
45 |
ላለፈው ክረምት ቤት አይሰራለትም |
46 |
የፈሰሰ ውሀ አይታፈስም |
47 |
አትሩጥ አንጋጥ |
48 |
መቀመጥ መቆመጥ |
49 |
ካለ ፈጣሪ አሟጠሽ ጋግሪ |
50 |
የትም ፍጪው ዱቄቱን አምጪው |
51 |
ስጋ ቁጠር ቢሉት ጣፊያ አንድ አለ |
52 |
ለጥምቀት ያልሆነ ቀሚስ ይበጣጠስ |
53 |
አወቅሽ አወቅሽ ቢሏት መጽሀፍ አጥባ ቆየች |
54 |
የምጣዱ እያለ የእንቅቡ ተንጣጣ |
55 |
እሱ የከፈተውን ጉሮሮ ሳይዘጋው አያድርም |
56 |
ፍየል ከመድረሷ ቅጠል መበጠሷ |
57 |
አለባብሰው ቢያርሱ በአረም ይመለሱ |
58 |
ንገረው ንገረው እምቢ ካለ መከራ ይምከረው |
59 |
አታግባና የሰው አጥር ዝለል |
60 |
ከስስታም አንድ ይወድቀው አንድ ይተርፈው |
61 |
ዶሮን ሲያታልሏት በመጫኛ ጣሏት |
62 |
ቀስ በቀስ እንቁላል በእግሩ ይሄዳል |
63 |
አተርፍ ባይ አጉዳይ |
64 |
አልጠግብ ባይ ሲተፋ ያድራል |
65 |
የልጅ ነገር ሁለት ፍሬ አንዱ ብስል አንዱ ጥሬ |
66 |
ያጣ ለማኝ ተሳድቦ ይሄዳል |
67 |
ሀምሳ ሎሚ ለአንድ ሰው ሸክሙ ለሀምሳ ሰው ጌጡ |
68 |
እውነቱን ተናግሮ ካመሹበት ማደር |
69 |
ድር ቢያብር አንበሳ ያስር |
70 |
ሆድ ያባውን ብቅል ያወጣዋል |
71 |
ከእጅ አይሻል ዶማ |
72 |
በእንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ |
73 |
የአህያ ባል ከጅብ አያስጥል |