Demeke Zewdu

ሰላማዊ ትግልና የኮ/ል ደመቀ ዘውዱ መንገድ

በአበራ ገ/ማርያም ኮ/ል ደመቀ ዘውዱ የወልቃይት ኮሚቴ መስራችና መሪ ናቸው። ካለማጋነን የወልቃይትን ትግል ከኮ/ል ደመቀ መነጠል፣ ክርስትናን ከክርስቶስ የመነጠል ያህል ነው። የወልቃይት ኮሚቴ በዘመነ ወያኔ እልህ አስጨራሽ የሰላማዊ ትግል አካሂዷል። አሁን ደግሞ ከሰላማዊ ትግሉ በተጨማሪ፣ ህዝቡን አንቅቶ፣ አደራጅቶ፣ አሰልጥኖ፣ አስታጥቆ፣ የተከዜ ዘብ ገንብቶ፣ ወልቃይትን ከማናቸውም የወያኔ ወረራ ለመመከት በንቃት እየተጠባበቀ ይገኛል። ኮ/ል ደመቀ በአንድ ወቅት እንደተናገሩት፣ እንደ በፊቱ ወልቃይት በወያኔ ወራሪዎች ተይዞ አይደለም እያለቃቀሱ ያሉት። አሁን ላይ መሬታቸውን በእጃቸው ይዘው፣ […]